የጽድቅ ውሳኔና በረከት
ይህ ጽሁፍ የሚያተኩረው ዳን 1፡1-10 ላይ ነው፡፡
መግቢያ ነጥቦች ፡-
- እስራኤላውያን በባቢሎናውያን መማረክና መወሰድ
------->የእግዚአብሄር ፈቃድ ነበረ(ኤር
27፡6)
- የዳንኤል የጽድቅ ውሳኔ “እንዳይረክስ በልቡ አሰበ”
-------->ይህ ውሳኔ እጅግ ጠቃሚ
ውሳኔና የዳንኤል የስኬት ምንጭ ነበር
ዳንኤል እንዳይረክስ በልቡ ያሰበው ፡-
- የብሉይ ኪዳንን ህግጋት ጠንቅቆ ያውቅ ስለነበረ ነው
- ለጣኦት የተሰዋ ምግብ እንደሚያረክሰው ስለሚያውቅ ነበር
- ለጣኦት የተሰዋን ምግብ መብላቱ ቃል ኪዳኑን መስበር እንደሆነም ስላሰበ ነበር
- ይህንን ውሳኔ ደግሞ በእግዚአብሄር ጸጋና ረድኤት አደረገው
ዳንኤል እና ጓደኞቹ በባቢሎን ነበሩ ነገር ግን የባቢሎን አልነበሩም፡፡ውስጣዊ ለውጥ (inner
conviction) ውጫዊ ጫናን ያሸንፋልና ነው፡፡ጉልህ የሚታዩ ትምህርታዊ ነጥቦች፡-
- የእግዚአብሄር ሉአላዊነት በዚህ ክፍል ውስጥ በሚገባ ታይቷል
- የእግዚአብሄር በፈተና ውስጥ ያለው አቅርቦት እና ረድኤት በሚገባ ተስተውሏል
- የዳንኤል ዲሲፕሊን ፡‹‹አሰበ›› በእንግሊዝኛው ‹‹he purposed in his heart>> ማለትም የምናስበው ነገር የምናደርገውንና ምርጫችንን እንደሚወስን ያስገነዝበናል
- ዳንኤል ክፉውንና መልካሙን የመለየት ችሎታ(discernment) ነበረው
- ዳንኤል ጽናት ነበረው፡-ዋናው ቁም ነገር መጀመራችን ሳይሆን መጨረሳችን ነው
ከተወሰዱት እርምጃዎች የተነሳ የታዩት አዎንታዊ ለውጦች፡-
- ዳንኤል በባቢሎን ኢምፓየር ከፍ አለ
- ትልልቅ አስደናቂ ትንቢቶችን ተቀበለ
- እየሱስ ያጸደቀው ነቢይ ሆነ ማቴ 24፡15
- ከእነ ኖህና እዮብ ጋር ሁሉ ተቆጠረ እዝ 14፡14
- ጓደኞቹ በየአውራጃው ላይ ተሾሙ ዳን 2:49
ነገር ግን ሊታወቅ የሚገባው ነገር የዚህ ሁሉ ክስተት ባለቤት ደራሲ እግዚአብሄር ነበረ፡፡በእኛም ህይወት ደራሲው
እሱ ነው፡-
- እግዚአብሄር እራሱ አሳልፎ ሰጣቸው ዳን 1፡2
- እግዚአብሄር እራሱ በባለስልጣኞቹ ፊት ሞገስን ሰጣቸው
- እግዚአብሄር ጥበብን፤ችሎታንና ማስተዋልን ሰጣቸው ዳን 1፡17
ስለዚህ በአለም ምናምንቴ ነገር እንዳንረክስ፤በእግዚአብሄርም በሰውም ፊት ሞገስ እንድናገኝና ጥሩ የህይወት ምስክርነት
እንዲኖረን ሶስት ነገሮችን እናድርግ ፡-
- ባላጋራችን ዲያቢሎስ የሚውጠውን ፈልጎ(ሊያረክሰን) እንደሚያገሳ አንበሳ በዙሪያችን ይዞራልና ጸንተን እንቃወመው
- ይህንን አለም እንዳንመስልና እንዳንወሰድ በልባችን መታደስ እንለወጥ ፡-ቃሉን እናጥና፣እናሰላስል፣እናስብ
- በዙሪያችን ብዙ የሚያረክሱ ነገሮች አሉና እንንቃ ብሎም ጨክነን እምቢ እንበል፡-በዚህ ዙሪያ ጸጋ እንዲበዛልን ጠንከር ያሉ ጸሎቶችን እንጸልይ
እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትን ሶስት እርምጃዎች ብንተገብር በሰዎች ላይ ልዩ የህይወት ተጽእኖና ምስክርነት ይኖረናል፡፡እግዚአብሄር
ሆይ እርዳን!
No comments:
Post a Comment